Wednesday, April 30, 2014

‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታችሁን ለመታደግ በሃይማኖት ጸንታችሁ መንፈሳዊ ተጋድሎ አድርጉ›› አለቃ አያሌው ታምሩ

 ‹‹ዛሬ በከፍተኛ አዘቅት ውስጥ የወደቀችው አገራችሁን ኢትዮጵያን እና ሃይማኖታችሁን ለመታደግ በሃይማኖት ጸንታችሁ መንፈሳዊ ተጋድሎ አድርጉ››  አለቃ አያሌው ታምሩ ሚያዚያ 23 ቀን 1983 የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአል በገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተ ክርስቲያን በሚከበርበት ጊዜ በቦታው ተገኝተው ያስተማሩት ትምህርት፡፡

(አንድ አድርገን ሚያዝያ 23 2004 ዓ.ም )-  የዛሬ 22 ዓመት መንግሥትና ቤተክህነት ሁለቱም የተሳሳተ ጎዳና ላይ ሳሉ አለቃ አያሌው ታምሩ በቅዱስ ጊዮርጊስ አውደ ምህረት ላይ ያስተማሩትን ትምህርት እንመልከት:: 

1983 ዓ.ም ደርግ በህዝቡ ላይ ሲሰራ የነበረው ግፍ ሁሉ ዘንግቶ ከመጣበት የውድቀት ጥሪ ለመዳን በከፍተኛ ደረጃ በተፍጨረጨረበት ዓመት ነበር ።። በቀደሙትዓመታት ሙልጭ አድርጎ ሲሰድባቸው የነበሩት ቀደምት የኢትዮጵያ ነገስታት ይልቁንም እነ አጤ ቴዎድሮስን ፡ እነ አጤ ዮሐንስን ፣ አጤ ምንይልክን በተለያዩ የመገናኛ ብዙሀን እያነሳ የህዝቡን ወኔ መቀስቀሻ እና የዘመቻ ማዘጋጃ ዘዴ ብሎ ይዞ ነበር።። ነጋ ጠባ ስለ እነዚህ ቀደምት ነገስታት ጀብዱና ሀገር ወዳድነት አትንኩኝ ባይነት ብዙ ይባል ነበር። ሚያዚያ 23 ቀን 1983 የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ በአል በአራዳ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን በሚከበርበት ጊዜ አለቃ አያሌው ታምሩ በቤተክርስቲያኑ ተገኝተው እንዲያስተምሩ ተጋብዘው ነበር። እሳቸው ስለ ሰማዕቱ ተጋድሎና በሃይማኖት ስላገኝው የድል አክሊል ዘርዝረው እንዲህ ብለው አስተማሩ።

አትሌት ቀነኒሳ ስላጋጠመው አደጋ ሲናገር



(አንድ አድርገን ሚያዚያ 23 2006 ዓ.ም)፡- ታዋቂው የረዥም ሩጫው ንጉስ ቀነኒሳ በቀለ April 27/2014 ምሽት EBS የቴሌቪዥን ጣቢያ በሰይፉ ፋንታሁን ሾዎ ላይ በአሜሪካን ሀገር ካለበት መኪና ከበስተኃላ በደረሰበት ግጭት ከኋላ ያለውን የመኪናው ክፍል ከፍተኛ ጉዳት ቢደርስበትም በሰው ላይ የደረሰ አንዳችም ጉዳት አልነበረም፡፡ አትሌት ቀነኒሳ ሲናገር ከምንም በላይ የገረመኝ ምንጊዜም በጉዞዬ የማይለዩኝ የእመቤታችን የቅድስት ድንግል ማርያምና የሊቀ መላዕኩ የቅዱስ ሚካኤል ምስሎች በፍሬም ውስጥ ይዤ ነበር በዚያ አስከፊ አደጋ የድንግል ማርያምም ሆነ የቅዱስ ሚካኤል በፍሬማቸው መስታዎት ላይ ስብራት ኣይደለም ጭረት እንኳን አለመኖሩ የሚገርም ነገር ነው ብሏል››

Friday, April 25, 2014

‹‹ይህ የእግዚአብሔር ድንቅ ሥራና የእነዚያ አባቶች በረከት መሆኑን እናምናለን››



  • ቀድሞ አፍሮ አይገባም መስቀልና እንዲሁም የጣና ቂርቆስ ገዳም የቅዱስ ያሬድ መስቀል  ወደ ኢትዮጵያ መመለሳቸው ይታወቃል፡፡
ቪዲዮውን በዚህ ይመልከቱ
(አንድ አድርገን ሚያዚያ 18 2006 ዓ.ም)፡-19ኛው ምእት ዓመት አካባቢ ከሰሜን ሸዋ እንደተወሰደ የሚነገርለት የመድኃኔዓለም ታቦት ዓርብ ሚያዝያ 17 ቀን 2006 .. ከጂቡቲ ወደ ኢትዮጵያ እንደገባ ለማወቅ ተችሏል፡፡በርግጥ ታቦቱ መቼ እንደተወሰደ፣ በማን እንደተወሰደና እንዴት እንደተወሰደ እየተጣራ ቢሆንም ወደ ኢትዮጵያ ሲመለስ ቦሌ አየር ማረፊያ ላይ አቀባበል ተደርጐለታል ጠቅላይ ቤተ ክህነት ሙዚየም ውስጥ የሚቀመጥ ይሆናል፡፡

Wednesday, April 23, 2014

ባለፉት 40 ዓመታት ለቤተክርስቲያን ‹‹ዘመነ ደርግ ረመጥ ፤ ዘመነ ኢሕአዴግ ዳጥ ››


·        በዘመነ ደርግ ሲኖዶስ እንዲበተን ተደርጓል ፤ መስቀል ለጨረታ ቀርቧል ፤ ፓትርያርኩ የሕይወት መስዋዕትነትን ስለ እምነታቸው ተቀብለዋል ፤ አብያተክርስቲያናት ተዘግተዋል ፤ የምዕመናን መንፈሳዊ ሕይወት ፈተና ላይ ወድቋል ፤  ……

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 16 ፤ 2004 ዓ.ም )፡- የኢትዮጵያ ቤተ ክርስትያን ክብር ባህል እምነትና ስርዓት መንግሥትና ቋንቋ ያቋቋመች የማትናወጥ ከመሆኗ ጋር ከሔኖክ ፤ ከኖህ ፤ ከመልከ ጼዴቅ ከነብያትና ከሀዋርያት ተላለፈውን ትምህርት ስርዓት ፤ እምነት ከትውልድ ወደ ትውልድ ስታስተላልፍ የኖረች በማስተላለፍ ላይ ያለች ፎኖተ ህይወት መሆኗ የተረጋጠ ነው፡፡ ቅዱሳን አበውን ፤ ኃያላን ነገስታትን ፤ ልዑላን መሳፍንትን ፤ ክቡራን መኳንንትን ፤ ዐይናሞች ሊቃውንትን በስጋ በነፍስ ወልዳ ያሳደገች ፤ የሌላ የማትፈልግ የራሷ የማትለቅ ዕጥፍ እናት ፤ ስንዱ እመቤት ናት፡፡(አለቃ አያሌው ታምሩ)

በቅዱስ መጽሐፍ ስለ ቅድስናዋ እግዚአብሔር ደጋግሞ የመሰከረላት አገራችን ኢትዮጵያም ቅድስት ክብርት ሐገር ናት ፡፡ ሰይጣን በእባብ አድሮ አዳምንና ሔዋንን እንደተዋጋቸው ሁሉ በልዩ ልዩ ሥጋውያንና መንፈሳውያን የውጭ ጠላቶች አድሮ ኢትዮጵያን ሲዋጋ ኖሯል፡፡  ዛሬም በመዋጋት ላይ ነው ፡፡ ነገር ግን የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ትጥቋን አጥብቃ ከቆመች ሳታርፍ ፤ ከዘረጋች ሳታጥፍ በኖረችበት ዘመን ሁሉ ኢትዮጵያ ሳትደፈር ኖራለች፡፡ በ10ኛው መቶ ዓመት የጉዲት ወረራ ፤ የ16ኛው መቶ ዓመት የግራኝ ወረራ ፤ ከ17ኛው እስከ 20ኛው መቶ ዓመት ተደጋግሞ የደረሰው የካቶሊክ ፤ የፕሮቴስታንት ፤ የቱርክና የግብጽ እስላማዊ ወረራ ተደጋግሞ የከሸፈው ባልተበረዘውና ባልተከለሰው የኢትዮጵያ  ቤተ ክርስቲያን  የእምነት ኃይል ነው፡፡ የአምስት ዓመት የፋሽስት ወረራም ጉዳት ማድረሱ የታወቀ ቢሆንም ከስሩ የተነቀለው ፤ ቁጥቋጦው የተመለመለ ፤ እንደ አንበጣ በዝቶ የመጣው የፋሽስት ሰራዊትም የውሀ ሽታ ሆኖ የቀረው በኢትዮጵያ ቤተክርስቲያን የእምነት ኃይልና በልጆቿ ደም ነው፡፡

የአቡነ ማትያስ የግብፅ ጉብኝት ተራዘመ


(ሪፖርተር  ሚያዚያ 15 2006 ዓ.ም) በግብፅ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን በተደረገላቸው ግብዣ መሠረት በመጪው ዓርብ ግብፅን ለመጐብኘት ዕቅድ የነበራቸው የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ፣ ጉብኝታቸውን ላልተወሰነ ጊዜ እንዲራዘም የግብፅ ቤተ ክርስቲያን መጠየቋን ምንጮችን በመጥቀስ የግብፁዴይሊ ሳባህጋዜጣ ዘገበ፡፡ 

Tuesday, April 22, 2014

የኢፌድሪ ፕሬዝዳንት ዶ/ር ሙላቱና ቤተሰቦቻቸው በሰንበት በቤተመንግሥት ግቢ በምትገኝው ቤተ ክርስቲያን እንደሚስቀድሱና ከቤተሰቦቻቸው ጋርም እንደሚቆርቡ ተገለጸ


  • ፓትርያርኩ ተገኝተው ፀሎተ ቅዳሴውን መርተው አገልግለውበታል፡፡ 
በብሔራዊ ቤተመንግሥት ቅጽ ውስጥ በምትገኝውና በደብረ ገነት ቅድስት ልደታ ለማርያም ቤተ ክርስቲያን ፕሬዝዳንቱ እና ቤተሰቦቻቸው በእለተ እሑድ በሚከናወነው ፀሎተ ቅዳሴ  እየተሳተፉ ቅዱስ ቁርባን እንደሚቀበሉ ተገለፀ፡፡

ኢሕአዴግ አደረጃጀቶቹ ስለ አክራሪነትና ጽንፈኝነት ያላቸውን ግንዛቤና አቋም የሚያዳምጥበትን ውይይት እያካሔደ ነው

  • በማኅበረ ቅዱሳን ላይ የተሰነዘረውን አክራሪነትን ፍረጃ ተሳታፊዎቹን አስቆጣ
  • ፍረጃው ለውይይቱ አካሄድ ከተቀመጠው አቅጣጫ ውጪ ነው ተብሏል፡፡
  • ‹‹ መንግሥት ማኅበረ ቅዱሳን አክራሪ ለመሆኑ አስገራሚ አስገራሚ ማስረጃዎች አሉት›› በስብሰባው ላይ የተነሳ ፍረጃ እና ክስ
  • ጠባብነት በሙስሊሞች አካባቢ ፤ ትምክህተኝነት በኦርቶዶክሶች አካባቢ የመዳበር ባህሪ አለው ተብሏል፡፡

(አፍሮ ታይምስ ሚያዚያ 14 2006 ዓ.ም)፡-  ገዥው ግንባር ኢሕአዴግ በሃይማኖት ይሁን በማንኛውም ሽፋን የሚደረግን የፖለቲካ ግጭት ለመመከት በሚል በአዲስ አበባ በተለያዩ በደረጃጀቶች ውስጥ ከታቀፉ አባሎቹ ጋር ውይይት በማካሄድ ላይ መሆኑ ተገለጸ፡፡  በአዲስ አበባ 116 ወረዳዎች ካሉት ሰባት የግንሩ አደረጃጀቶች ማለትም የሴቶች ፤ ወጣቶች ፤ መምህራን ፤ መንግሥታዊና መንግታዊ ያልሆኑ ድጅቶች ፤ የአነስተኛ እና ጥቃቅን ተቋማት ከእያንዳንዳቸው 60 አባላት ያሳተፈ ውይይት ባለፈው ሳምንት መጨረሻ እንስቶ በመካሔድ ላይ ይገኛል፡፡

Sunday, April 20, 2014

የንግድና የኑፋቄ ስራን ለመስራት የተቋቋሙ ማኅበራት ‹‹ማኅበረ ወይንዬ›› እንደማሳያ



  • ‹‹ማኅበረ ወይንዬ›› የተባለው የንግድ ተቋም የታገደበት ደብዳቤ ከቤተክህነት መዝገብ ቤት ሊገኝ አልቻለም፡፡
  • ጸረ-ግብረሰዶማውያን ሀገራዊ ንቅናቄ ሃሳብ የተነሳው ከቤተክህነቱ ሆኖ ሳለ አቶ ደረጀ የራሱ በማስመሰል ሕጋዊ በመምሰል ከመስተዳደሩ ጋር ስራ ሲሰራ ነበር፡፡

(አንድ አድርገን ሚያዚያ 13 2006ዓ.ም )፡- የቀለም ቀንዱ አለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ እንደተረጎሙት ማኅበር ማለት ‹‹በቁሙ አንድነት ፤ ሸንጎ ፤ ብዙ ሰው ›› ማለት ነው ፡፡ በሌላም አተረጓጎም ‹‹ወገን ፤ ነገድ ፤ ቤተሰብ ፤ ጭፍራ ፤ ሰራዊት›› የሚል ትርጓሜ ተሰጥቶታል ፡፡ ጠቅለል ባለ መንገድ ማኅበር አንድነትና ህብረትን የሚያመላክት ነገር ነው፡፡ ቤተክርስትያናችንም ወጣቶች በሰንበት ትምህርት ቤት ፤ አዛውንቶች ደግሞ በሰንበቴ ማኅበራት በመታቀፍ አንድነታቸውን የሚፈጽሙበት ሁኔታ አመቻታላችዋለች ፡፡በዚህም ከ50 ዓመት በላይ ስትሰራበት ቆይታለች ነገር ግን ከ1980 ወዲህ ቤተክርስትያኗ አስቀድማ ካስቀመጠችው አወቃቀር የተለየ በተለየ በ1990 ዎቹ መጨረሻ የማበራት ቁጥር እጅግ እየበዛ መጥቷል፡፡ መልካም ስራ ያላቸው ማኅበራ ቢኖሩም በብዛት በቤተክርስትያኗ መዋቅር ስር አይደሉም ፤ መልካም ስራቸውንም በአደባባይ ማሳየት አልቻሉም ፤ ቅዱስ ሲኖዶስም አያውቃቸውም ፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ ቤተ ክርስቲያን ግብረ ሰዶማዊነትን እስከ መጨረሻው አምርራ ትዋጋለች አሉ


  • ‹‹ፀረ ግብረ ሰዶማዊነት የመንግሥት አጀንዳ ሳይሆን የተወሰኑ ቡድኖች አጀንዳ ነው ስለዚህም በሕግ የተቀመጠው ቅጣት በቂ ነው››  አቶ ሬድዋን ሁሴን ለአሶሼትድ ፕሬስ

(ሪፖርተር ሚያዚያ 12 2006 ዓ.ም) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ፓትርያርክ፣ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ፣ ኢትዮጵያውያን ግብረ ሰዶማዊነትን በጽናት እንዲመክቱ ጥሪ አቀረቡ፡፡ ቤተ ክርስቲያንም እስከመጨረሻው አምርራ ትዋጋለች አሉ፡፡

ቅዱስ ፓትርያርኩ 2006 .. የትንሣኤን በዓል ምክንያት በማድረግ ‹‹ሕይወትን አየናት፣ አወቅናትም›› በሚል መሪ ቃል ባስተላለፉት ሃይማኖታዊ ቡራኬ ላይ እንዳሳሰቡት፣ ሰዶምንና ገሞራን በእሳት ያጋየ ግብረ ኃጢአት በኢትዮጵያ ልማትና ዕድገት ሳይሆን መቅሰፍትና ውድቀት እንዳያስከትል ሁሉም ኢትዮጵያዊ ይህንን የሰዶም ግብረ ኃጢአት ሊከላከል ይገባል፡፡

Saturday, April 19, 2014

በቅዱሳን ስም ፤ የእግር ኳስ ክለቦችና ቢራ ፋብሪካዎች


  • ‹‹ቅዱስ ቂርቆስ›› የስፖርት ክለብ የሚል ቡድን ተቋቁሞ በአዲስ አበባ ሊግ ውድድሩን እያደረገ ይገኛል፡፡
(አንድ አድርገን ሚያዚያ 10 2006 ዓ.ም) ፡- በ1915 ዓ.ም የቅዱስ ጊዮርጊስ ቢራ ፋብሪካ ስራ መጀመሩንናቀጥሎ ከ77 ዓመት በፊት ኢጣልያ ኢትዮጵያን በወረረችበት ወቅት በ1928 ዓ.ም አራዳ(ፒያሳ) አካባቢ ባሉ ወጣቶችና ጥቂት በጎ አድራጊዎች አማካኝነት የቅዱስ ጊዮርጊስ የስፖርት ክለብ እነደተመሰረተ የኋላ ታሪኩ ይናገራል፡፡ 

አሁን እኛ የክለቡን የኋላ ታሪክ ለአንባቢያን ለማስተዋወቅ ሳይሆን በቅዱሳን ስም የቢራ ፋብሪካ እና የእግርኳስ ክለቦች ቀድሞ መኖር እና አሁንም መፈጠር መቻል ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ እምነት አኳያ እንዴት ይታያል የሚለውን ለማመላከት ነው፡፡ ከጥቂት አመታት በፊት በ‹‹ቅዱስ ጊዮርጊስ›› ስም ቢራ ማምረት መቻልን የተቃወሙ ጥቂት ወጣቶች ይህን ስም የማስቀየር ዘመቻ ጀምረው ነበር ፤ ወጣቶቹ አላማቸው ለተዋህዶ እምነት ጤዛ ልሰው ድንጋይ ተንተርሰው ፤ እንደ ሻማ ቀልጠው ወንጌልን ለአለም ለማድረስ በርካታ መስዋእትነትን የከፈሉ በጻድቃን ሰማዕታት ስም የእምነቱ አስተምህሮ የማይደግፈውን የረከሰ ተግባር ለቢራ ማሻሻጫነት ስማቸውን መጠቀም መቻል የለበትም የሚል ጥቅል ሃሳብ ነበረው ፤ ቀጥለውም ስማቸው ቤተክርስቲያኒቱ ከማክበሯ በላይ በሕግ አግባብ ማንም እንዳይጠቀምበት ከማድረግ በተጨማሪም ‹‹ቅዱስ ጊዮርጊስ›› የሚለውን ለቢራ መጠሪያ የሚጠቀመውን ፋብሪካ ስሙን እስከማስቀየር የሚያስችል ዘመቻ ነበር፡፡

Friday, April 18, 2014

የመዝሙር ጥራዝ ፤ የበዓል ስጦታ


አንድ አድርገን ሚያዚያ 5 2006 ዓ.ም) ፡- በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስተ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ሥርዓት በየወቅቱ የሚዘመሩ መዝሙራት መኖራቸው ይታወቃል፡፡ እነዚህ መዝሙራትም በመጽሐፍ መልክ ተዘጋጅተው የሰንበት ተማሪዎች እና ምዕመኑ ዘንድ ለማድረስ ተሞክሯል ፡፡ እነዚህ ከስድስት መቶ የሚበልጡ መዝሙራት በሀገር ውስጥ እና ከሀገር ውጪ ለሚኖሩ የሰንበት ትምህርት ቤት ተማሪዎች እና ምዕመናን ተደራሽ ለማድረግ ያስችል ዘንድ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያንን የጠበቁትን  በመስቀል ፤ በልደት ፤ በጥምቀት ፤ በስቅለት ፤ በትንሳኤ ፤ በጰራቅሊጦስ  እና መሰል የቤተክርስቲያን ዋና ዋና በዓላት በተጨማሪ ስለ ድንግል ማርያም ፤ ስለ ቅዱሳን ፤ ስለ ንስሃ ስለ ጾም ወቅቶችን መሰረት አድርገው የሚዘመሩ ከ237 በላይ መዝሙራትን በpdf ብሎጋችን ላይ ለጥፈንልዎታል፡፡
መልካም የትንሳኤ በዓል ይሁንላችሁ